Wednesday, 23 July 2014

ማነው የታሰረው?



 
አቦ ታሰረች፣ ታሰረች፣ ታሰረች፣ ታሰረች አትበሉኝ!!!

እኛ ሰልፍ አትውጡ ስንባል ከቤታችን የማንወጣ፣ እጅ ስጡ ስንባል እግራችንንም የምንመርቅ፣ አትፃፉ ስንባል ብዕራችንን የምናስረክብ፣ አትዩ ስንባል አይናችንን ጨፍነን ጀሮአችንን የምንይዝ  ያለእጅ የታፈንን እና ያለካቴና የታሰርን እያለን እርሷ ታሰረች አትበሉኝ፡፡

እርሷማ እንኳን ደስ ያለን ነፃ ወጣች እንጂ አልታሰረችም፡፡ በብርታቷ፣ በፅናቷ እና በጀግንነቷ ነፃ ወጣች፡፡ እርሷማ ነፃነቷ በደሟ የዋጀችና በእጇ ስብራት የባርነት ቀንበርን የሰበረች ጀግና ናት፡፡ እርሷማ አካላዊ መከራን ተቀብላ መንፈሳዊ ነፃነቷን አገኘች፡፡ 

ታዲያ የትኛው ነው የነፃነት መንገድ? የወይኒ መንገድ ወይስ አሁን እኛ ያለንበት መንገድ?

ዲሞክራሲን እንጂ ነፃነታችንን ከምርጫ ኮሮጆ አንጠብቅ፡፡ ነፃነት ሳይኖር ዲሞክራሲ ሊኖር አይችልም፡፡ ነፃነትን ለማግኘት አቅጣጫችንን ወደ ቤተመንግስት ሳይሆን ወደ እስር ቤቶች እናድርግ፡፡ ‹‹የነፃነት ጉዞ ወደ እስር ቤት›› ብለን እናውጅ፡፡ እንሂድ እስር ቤትን እንሙላ፡፡ በዚህ ወቅት ‹‹አቤቱ ጓደኛዬን ፍታልኝ›› የሚል የፈሪ ፀሎት አይሰራም፡፡
የነፃነት ጉዞ ወደ እስር ቤት

No comments:

Post a Comment