Friday, 16 May 2014

የሚታገሉትን የማያውቁ ታጋዮች





የተቃዋሚ ባንዲራ ማውለብለብ እና በተቃዋሚ ፓርቲ ጃንጥላ ስር መጠለል ብቻ ተቃዋሚ አያሰኝም፡፡ የሰማያዊንም ሆነ የአንድነትን ባንዲራ እያውለበለቡ ከወያኔ አስተሳሰብ የማይለይ አስተሳሰብ የሚያራምዱ መኖራቸውን የሚካድ አይደለም፡፡ መጀመሪያ ትግል ከመጀመሩ (ከመታሰቡ) በፊት ‹‹ማንን፣ ለምን እና እንዴት ነው የምንታገለው?›› ብሎ እራስን መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡

የምንታገለው ኢህአዴግን ወይስ አስተሳሰቡን?
እኔ የምታገለው አስተሳሰብን ነው፡፡ ማሸነፍም የምፈልገው አስተሳሰቡን ነው፡፡ ኢህዴጋዊ አስተሳሰብን ማሸነፍ ካቻልን ለውጥ ማምጣት አይቻልም፡፡ ኢህአዴግ ብቻ ሳይሆን ኢህአዴጋዊ አስተሳሰብ መወገድ አለበት፡፡ ይህንን አስተሳሰብ የሚያራምዱ ኢህአዴግ ውስጥ ብቻ ነው ያሉት ብሎ ማመን የዋህነት ሳይሆን ጅልነትም ነው፡፡ ይህንን አስተሳሰብ የሚያራምዱ ማንኛውንም ግለሰብም ሆነ ቡድን ሰማያዊም ሆነ አንድነት ውስጥ ይኑር ኢህአዴግ ውስጥ ካለው ባልተለየ መልኩ መታገል ተገቢ ነው፡፡

ይህ ካልሆነ የምንታገለው ‹‹ለምን እነርሱ ብቻ 23 አመት ሙሉ ጨቆኑን?›› ከሚል ሰንካላ እኩይ አስተሳሰብ በመነሳት ጨቋኝን በሌላ ጨቋኝ መተካትን አላማ ያደረገ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ዋጋ የሌለው ምንም አይነት መሰዋዕትነት ሊከፈልበት የማይገባ ትግል ነው፡፡ ይህንን አይነት ትግል ደግሞ የትም አያደርስም፡፡

ስንታገል ‹‹ይህንን ህዝብ እንዴት ከባርነት ነፃ እናውጣው?›› ከሚል መነሾ በመነሳት እንጂ እንዴት በዚህ ህዝብ ላይ ሌላ የባርነት ቀንበር እንጫንበት ከሚል አስተሳሰብ መነሳቱ ትርጉም የለውም፡፡ ህዝባችን ባርነት ሆነ አገዛዝ ብርቁ አይደለም፡፡ ህዝባችን የናፈቀው ነፃነት ነው፡፡ ነፃነት እንደ ውሃ የጠማው ህዝብ ነው ያለን፡፡

ህዝባችን ባርነት፣ ጎጠኝነት… አንገሽግሾታል፡፡        
  

No comments:

Post a Comment